ለሀሙስ ዲሴምበር 1 መታወቅ ያለባቸው ስድስት ጉዳዮችን እነሆ! ስለ እግር ጉዞ የትምህርት ቤት አውቶቡስ ተነሳሽነት፣ ስለ መጪው የአእምሮ ጤና መድረክ፣ በሥራ ማስኬጃ በጀት ክዋኔ ሂደት እንዴት እንደሚሳተፉ፣ የረጅም ጊዜ የትምህርት ቦርድ አባል ዶ/ር ጁዲዝ ዶካ (Dr. Judith Docca) ጡረታ መውጣት መረጃ ፣ ስለ መጥፎ የአየር ሁኔታ መረጃ ማሳሰቢያዎች፣ እና ሁለት የእግር ኳስ ቡድኖች በዚህ አመት የስቴት ሻምፒዮና ስለ መድረሳቸው መረጃዎች ተካተዋል።
በዚህ ሳምንት ሁለት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፉትቦል ቡድኖች ወደ ስቴት ሻምፒዮና የፍጻሜ ውድድር አልፈዋል!
የኩዊንስ ኦርቻርድ (QO) ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወደ 4A የስቴት ሻምፒዮና የፍጻሜ ውድድር አልፏል፥ እንዲሁም የደማስከስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወደ 3A የስቴት ፉትቦል ሻምፒዮና አልፏል። QO ኩዊንስ ኦርቻርድ ከቻርለስ ኸርበርት ፍላወርስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዛሬ፣ ሐሙስ፣ 7፡00 p.m. ይጫወታል። ደማስከስ ከኦካዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጋር ቅዳሜ 7፡00 p.m. ላይ ይጫወታሉ። ሁለቱም ጨዋታዎች በአናፖሊስ በሚገኘው የባህር ኃይል-ማሪን ኮርፕ ስታዲየም ይካሄዳሉ። በዚህ አስደናቂ ስኬት ለሁለቱም ቡድኖች እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን!
የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ
Montgomery County Public Schools
Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org