ውድ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ የማህበረሰብ አባላት
ይህንን የምጽፈው በአትሌቲክስ ዝግጅቶቻችን ላይ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ አካባቢ መኖሩን ለማረጋገጥ ባለፈው ሳምንት ያሳወቅናቸውን ድርጊቶች ክትትል ለማድረግ ነው። እነዚህን እርምጃዎች ስናስታውቅ፣ ትምህርት ቤቶቻችንን እና የአትሌቲክስ ፕሮግራሞቻችንን በመወከል ህብረተሰቡ ደህንነታቸው የተጠበቀ ሠላማዊ እና ምቹ እንዲሆኑ እንደሚጠብቅ በመገንዘባችን ነው።
ባለፈው አርብ፣ በጥሩ መንፈስ የተገነቡ፣ ከፍተኛ አቅም የሚጠይቁ፣ ተማሪ-አትሌቶች በከፍተኛ ደረጃ የሚወዳደሩበት እና ተመልካቾችን የሚያስደስቱ ጨዋታዎችን አይቻለሁ። ይህ አዎንታዊ ውጤት በአጋጣሚ የተከሰተ አይደለም። ተማሪዎቻችን እኩዮቻቸው ጥሩ ስፖርታዊ ጨዋነትን እና መከባበርን እንዲጠብቁ ጥሪ አድርገዋል፣ ሰራተኞች፣ ወላጆች እና በጎ ፈቃደኞች የመልካም ባህሪ ሞዴል አሳይተዋል፣ ሁሉም ሰው አስተማማኝ እና አስደሳች ተከታታይ የአትሌቲክስ ዝግጅቶች ላይ ያለምንም ስጋት ተዝናንቷል፣ እነዚህ የት/ቤቶቻችን ባህሎች አስፈላጊ አካል ናቸው።
ያንን የመሰለ ውጤት ለማግኘት ባለፈው ሳምንት ተግባራዊ ካደረግናቸው ዋና ዋና ለውጦች መካከል፡-
እነዚህ ፖሊሲዎች በጣም ልንመለከታቸው የሚገቡን ተግባሮች ላይ ያነጣጠረ መሆኑን እናምናለን። ተማሪዎች እና ወላጆች ትምህርት ቤታቸው በማይሳተፍባቸው ጨዋታዎች ላይ አዋቂ ሰው አብሯቸው ከሌለ መከታተል አለመቻላቸውን በተመለከተ አንዳንድ ስጋቶችን ሰምተናል። ተማሪዎች የሌሎች ትምህርት ቤቶችን ውድድር የማየት ፍላጎት ሊኖራቸው እንደሚችል ብንገነዘብም፣ በዝግጅታችን ላይ ካሉ ተማሪዎች ጋር መልካም ግንኙነት እንዲኖረን ፖሊሲዎቹ በሥራ ላይ መዋላቸውን ማስረዳት አስፈላጊ ነው። ለማንኛውም ክስተቶች ምላሽ ለመስጠት መልካም ግንኙነቶች በጣም አስፈላጊው መሳሪያ ናቸው። የአትሌቲክስ ደህንነት ፕላን ላይ በተገለጹት የውሳኔ መመሪያዎች መሰረት ፕሮግራማችንን እና
ክስተቶችን መከታተል እና መገምገም እንቀጥላለን። ሌሎች የአካባቢ ዲስትሪክቶች ተመሳሳይ እቅዶችን በመተግበር ላይ ሲሆኑ በእኛ በኩል ደህንነትን ለማረጋገጥ የተሻሉ ልምዶችን በማሳየት ረገድ ግንባር ቀደም ነን።
የበለጠ መረጃ ለማግኘት፥ እባክዎ ወቅታዊ R.A.I.S.E ሪፖርት ይመልከቱ።
MCPS ወቅታዊ የአትሌቲክስ ጋዜጣ
ስለቀጣይ ድጋፍዎ እናመሰግናለን።
ከልብ
Monifa B. McKnight
Superintendent of Schools
Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org