ለተከበራችሁ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) ማህበረሰብ፦
የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ በተቀረው 2021-2022 የትምህርት ዓመት በአስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ምክንያት ትምህርት ቤቶች በሚዘጉባቸው ቀናት ወደ ቨርቹወል ትምህርት እንደሚሻገር ይገመታል። እነዚህ ቀናት ለሁሉም ደህንነት ሲባል የትምህርት ተቋማትን መዘጋት እንደሚያስፈልግ ስትሪክቱ የሚወስንባቸው ቀናት ናቸው። ይህ ውሳኔ የሚሰጠው እያንዳንዱን ሁኔታ በማጤን ነው።
መጥፎ የአየር ሁኔታ ሲተነበይ የ MCPS የመጓጓዣ እና የአመራር አካላት የአየር ሁኔታ ትንበያውን እየተከታተሉ ወደ ቨርቹወል ትምህርት የመሸጋገር ሁኔታ ካለ ለቤተሰቦች ያሳውቃሉ። ተማሪዎች ወደ ቤታቸው በሚመጡበት ጊዜ Chromebooks፣ቻርጀሮች እና ሌሎች የመማሪያ ቁሳቁሶችን ይዘው መምጣታቸውን እንዲያረጋግጡ ይጠየቃሉ። ሰራተኞችም ቨርቹወል የማስተማሪያ ቁሳቁሶች እና ዝግጅት እንዲኖራቸው ይጠየቃሉ።
MCPS ከትምህርት ተቋማት ጋር ለመገናኘት እና ወደ ቨርቹወል ትምህርት ስለመሸጋገር ለማሳወቅ የሚቻልባቸውን በርካታ መንገዶችን ይጠቀማል።እነዚህም የሚከተሉት ናቸው፡-
ይህ ገጽ አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ሲከሰት በሚከናወን ቨርቹወል የትምህርት ወቅት ምን እንደሚጠበቅ ለማስገንዘብ እንዲረዳዎት እና የቴክኒካዊ ድጋፍ ግብአቶችን ለመስጠት የሚያግዝ መረጃ የያዘ ነው።
ጠቃሚ ማስገንዘቢያዎች፦
የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ
Montgomery County Public Schools
Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org