ሐሙስ፣ ኤፕሪል 7 መታወቅ ያለባቸው ቁልፍ ጉዳዮችን እነሆ! በስፕሪንግ ዕረፍት ስለ ኮቪድ-19 ወረርሽኝ ጥንቃቈ፣ ስለመጪው የማህበረሰብ ውይይት ተሳትፎ፣ እና ሌሎችም አስፈላጊ ማሳሰቢያዎችን ያካትታሉ።
በእረፍት ጊዜዎ ይደሰቱ ነገር ግን በጥንቃቄ ራስዎን ይጠብቁ
ምንም እንኳን በሞንትጎመሪ ካውንቲ ውስጥ ፖዚቲቭ የኮቪድ-19 መጠን ዝቅተኛ ቢሆንም፣ በዚሁ እንዲቀጥል እና ኤፕሪል 19 ከኮቪድ-19 ተጽእኖ ነፃ ሆኖ ወደ ትምህርት ቤት ለመመለስ፣ በንቃት ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። በስፕሪንግ እረፍት ጊዜ እርስዎ ከኮቪድ-19 ነጻ ለመሆን ማድረግ ያለብዎትን ጥንቃቄ ዝርዝር ያስታውሱ? የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (CDC) ኮቪድ-19 ለመከላከል በስፕሪንግ ዕረፍት ማከናወን የሚችሏቸውን ቀላል ነገሮች ዝርዝር ይመክራል። የማህበረሰባችንን ጤንነት መጠበቅ የሁላችንም ሃላፊነት ነው።
ለተማሪዎች እና ለሰራተኞች ማሳሰቢያ፦ ከ MCPS በተሰጠው የኮቪድ-19 ከቤት- መመርመርያ ሰኞ፣ ኤፕሪል 18 ምርመራ ይውሰዱ
ስርጭት፡-
MCPS የኮቪድ-19 ፈጣን የቤት መመርመሪያ ቁሳቁሶችን እስከ ኤፕሪል 6 ድረስ አሰራጭቷል። የልጅዎን ቦርሳ ይመልከቱ።
የኮቪድ-19 መመርመሪያ ኪት አጠቃቀም መመሪያዎች፦
ቪዲዮ፡ የኮቪድ-19 ፈጣን መመርመሪያ መሣሪያ አጠቃቀም መመሪያ
በዚህ ድረገጽ ላይ የበለጠ ግንዛቤ ያግኙ፤ በራሪ ወረቀቶች ላይ ያለውን መመሪያ ያንብቡ።
እንግሊዘኛ / እስፓኒሽ / 中文 / ፈረንሳይኛ / ፖርቺጊዝ / ቻይንኛ / tiếng ቪትናም / አማርኛ
(ማሳሰቢያ፡ እነዚህ ከአፍንጫ ፈሳሽ በመውሰድ የሚከናወኑ ፈጣን መመርመርያዎች ናቸው፤ እባክዎን በመሳሪያዎቹ ውስጥ የተካተቱትን መመሪያዎች ይከተሉ።)
5 ዓመት እና ከዚያ በላይ እድሜ ያላቸው ግለሰቦች የኮቪድ-19 ክትባት መውሰድ ይችላሉ። ክትባቱ ደህንነቱ የተጠበቀ እና በነፃ የሚሰጥ ነው። MCPS ቅዳሜ፣ ኤፕሪል 9 የክትባት ክሊኒኮችን ያስተናግዳል። እንዲሁም የሞንትጎመሪ ካውንቲ የጤና እና የሰብአዊ አገልግሎት ዲፓርትመንት በስፕሪንግ ዕረፍት ጊዜ የክትባት አገልግሎት ይሰጣል። በ MCPS ድረገጽ እና DHHS ድረገጽ ላይ የበለጠ ግንዛቤ ያግኙ።
እንደተለመደው፣በማንኛውም የእረፍት ጊዜ ዓርብ ትምህርት ቤቶች ለእረፍት ከመዘጋታቸው በፊት፣ ተማሪዎች እና ሰራተኞች የሚጠቀሙባቸውን የትምህርት መሳሪያዎቻቸውን ወደ ቤታቸው እንዲወስዱ ት/ቤቶች ያሳስባሉ። የቻርጀር ገመዱን ጭምር ወደ ቤት እንዲያመጣ/እንድታመጣ ልጅዎን ያስታውሱ።
አዲሱ የማህበረሰብ ተሳትፎ ኦፊሰር (ዋና ስራ አስፈፃሚ) ፕሮግራም ስምምነት በቅርቡ ይፈረማል ተብሎ ይጠበቃል። ከስፕሪንግ ዕረፍት በኋላ ሲዘጋጅ፣ የማህበረሰብ መልእክት እንልካለን ጋዜጣዊ መግለጫም እንሰጣለን። ይህ አዲስ ስምምነት ሁሉንም ተማሪዎች እና ሰራተኞች የሚጠቅም ደህንነቱ የተጠበቀ፣አካታች እና ምቹ የትምህርት አካባቢን ለማረጋገጥ የተነደፈ አዲስ አቀራረብን የሚገልጽ ነው።
በጊዜያዊ ሱፐርኢንተንደንት ዶ/ር ሞኒፋ ቢ.ማክኒትን (Dr. Monifa B. McKnight) አማካይነት የሚካሄዱ ሶስት የማህበረሰብ ውይይቶች ላይ ይሳተፉ፦ ተማሪዎቻችንን ለማስቀደም አሁን ሁላችንም አንድ ላይ እንሁን! ኤፕሪል እና ሜይ ላይ የማህበረሰብ ውይይቶች ይደረጋሉ። በእነዚህ ዝግጅቶች ላይ ቤተሰቦች፣ ተማሪዎች፣ ሰራተኞች እና የማህበረሰብ አባላት MCPS እንዴት ተማሪዎቹን በተሻለ ሁኔታ ማገልገል እንደሚችል እና ስለ ዲስትሪክቱ ጥንካሬዎች ቅድሚያ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እና ስላሉት እድሎች ይወያያሉ።
ዝግጅቶቹ የሚከናወኑት፦
እነዚህ ውይይቶች በተከታታይ ከሚደረጉ የተሳትፎ ክንውኖች የመጀመርያዎቹ ሲሆኑ ወደፊትም ቨርቹወል በሚደረጉ ውይይቶች ላይ የመሳተፍ እድሎች ይኖራሉ። RSVP ለመሣተፍ እንዲመዘገቡ እናበረታታለን። የተወሰነ የ MCPS አውቶቡስ መጓጓዣ ይቀርባል። በጌትስርበርግ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት (Gaithersburg High School) ለሚደረገው የመጀመሪያው ፕሮግራም የ MCPS አውቶቡስ ዝግጅቱ ከመጀመሩ በፊት እና በኋላ "Gaithersburg High stopping at Montgomery Village Middle, Roberto Clemente Middle and Clarksburg High School መካከል ይመላለሳል።
Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org