ውድ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) ተማሪዎች፣ ቤተሰቦች እና ሰራተኞች
አሁን በክረምቱ የአየር ሁኔታ ወቅት መሀል ላይ ስለገባን፣ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) በከባድ/አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ወቅት የአሠራር ሁኔታን ለውጥ ማድረግ ሲያስፈልግ እና ት/ቤት መዝጋት እና ወደ ቨርቹዋል ማስተማር መሸጋገርን በሚያረጋግጥ ጊዜ ለማህበረሰቡ የማሳወቅ አሠራር ሂደቱን እያሻሻለ ነው። ሁኔታዎች ለተማሪዎች እና ለሰራተኞች ደህንነት አመቺ እንዳልሆኑ ሲታወቅ፣ ስድስት የክወና ሁኔታዎች አማራጮች አሉን፣ይህም አሁን በቀላሉ ለመረዳት በሚቻል፣
በቀለም በተቀመጠላቸው መልእክቶች ሪፖርት ይደረጋል። እነዚህም የሚከተሉት ናቸው፦
የተማሪዎች እና የሰራተኞች ደህንነት ተቀዳሚ ትኩረታችን ሆኖ ይቆያል፣ MCPS እነዚህ ሁኔታዎች ለቤተሰቦች እና ለሰራተኞች ሊያስከትሉ የሚችሉትን ችግር ይገነዘባል። በድንገተኛ የአየር ሁኔታዎች ምክንያት የአሠራር ለውጦችን ማድረግ አስፈላጊ የሚሆነው በጥንቃቄ ከተገመገመ በኋላ ብቻ ነው።
ውሳኔ በሚሰጥበት ጊዜ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) አመራር ከሀገር አቀፍ እና ከአካባቢ የአየር ሁኔታ ባለሙያዎች፣ ከአካባቢው የድንገተኛ አደጋ አስተዳደር ባለስልጣናት፣ እና ሌሎች የመንግስት እና የአጎራባች ትምህርት ቤቶች ዲስትሪክቶችን የስራ ሁኔታ ይገመግማል። በተጨማሪም አመራሩ ከስቴት ሀይዌይ አስተዳዳሪዎች መረጃን ይሰበስባል፣ የመንገዶችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) የመኪና ማቆሚያ ቦታዎችን እና የት/ቤት አውቶቡስ መጓጓዣ መስመሮችን ሁኔታ በሠራተኞቹ አማካይነት በመመርመር አስፈላጊነቱ ሲረጋገጥ ብቻ ውሳኔ ይሰጣል።
ቨርቹወል ትምህርት-Virtual Learning
ወደ ቨርቹዋል ትምህርት መሸጋገሩን የሚያመለክተው ሐምራዊ ኮድ በከባድ የአየር ሁኔታ ጊዜ መማር እና ማስተማር እንደሚቀጥል ያረጋግጣል። የሜሪላንድ ስቴት የትምህርት ዲፓርትመንት ይህንን እድል ለአካባቢው ትምህርት ቤቶች ያቀረበ ከመሆኑም በላይ የሞንትጎመሪ ካውንቲ የትምህርት ቦርድ ጃንዋሪ 12 በተካሄደው ቨርቹዋል የስራ ስብሰባ ላይ እቅዱን አጽድቋል። ያለው ቴክኖሎጂ እና የቀድሞው ቨርቹዋል የመማር ማስተማር ልምድ MCPS በአስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እና በድንገተኛ ጊዜም ቢሆን ከተማሪዎች ጋር መስራቱን እንዲቀጥል ያስችለዋል። ሰራተኞች እና ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ዝግጁ እንዲሆኑ አስፈላጊ መመሪያዎች አሉ። እነዚህ መመሪያዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦
የአየሩ ሁኔታ አሳሳቢ በሚሆንበት ጊዜ፣ MCPS በጊዜው እና በትክክለኛ መረጃ ወቅታዊ መረጃዎችን ማግኘትዎን ለማረጋገጥ ጥረት ያደርጋል። እባክዎ ከአየር ሁኔታ ጋር የተገናኙ የት/ቤቶች ዘግይቶ መከፈት፣ የት/ቤቶች መዘጋት እና ተማሪዎችን ቀደም ብሎ ማሰናበት የመሳሰሉትን መከታተል እና የተማሪዎቻችንን እና የሰራተኞቻችንን ደህንነት ለማረጋገጥ በምንሰራበት ጊዜ ከትምህርት ቤት ሰራተኞች ጋር መተባበርዎን ያረጋግጡ።
ParentVUE አካውንትዎን አዘውትረው ይመልከቱ፥ እና አስፈላጊ ከሆነ እርስዎ የሚገኙበትን መረጃዎን ያዘምኑ። ይህ ሁሉንም አስፈላጊ የትምህርት ቤት የስራ ሁኔታ ወቅታዊ መረጃዎችን እንደሚያገኙ ያረጋግጣል።
የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ
Montgomery County Public Schools
Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org