ሐሙስ ኖቬምበር 17 ማወቅ ያለብን ስምንት ጉዳዮችን እነሆ!

ሀሙስ ኖቬምበር 17 መታወቅ ያለባቸው ስምንት ጉዳዮች ከዚህ የሚከተሉት ናቸው፦ የት/ቤቶቻችንን የአውቶቡስ መስመሮችን ለመደገፍ ስለተወሰዱ ወሳኝ እርምጃዎች መረጃ፣ ስለ በጀት ሂደቱ ሌላ የውይይት እድል፣ 2022-2023 የዊንተር አትሌቲክስ ደህንነት እቅድ፣ ድምጽዎ ተሰሚነት ያለው መሆኑን እንዴት ማረጋገጥ እንደሚችሉ የሚገልጽ መረጃ፥ ስለ መጪው የትምህርት ዓመት አቆጣጠር/ካለንደር፣ ለወላጆች ESL ትምህርቶች፣ ተጨማሪ የመንገድ ማቋረጫ ጠባቂዎች ጥሪ፣ የተማሪዎቻችን በስፖርት እና በሙዚቃ አስደሳች ድሎች እና ስለ መጪው ትምህርት ቤቶች የሚዘጉባቸው ቀናት ማሳሰቢያዎች ይቀርባሉ።

  1. busየትምህርት ቤት አውቶቡስ መስመሮችን ለመደገፍ አዳዲስ እርምጃዎች ይፋ ተደርገዋል
    ሱፐርኢንተንደንት ዶ/ር ሞኒፋ መክናይት (Superintendent Dr. Monifa McKnight) አዳዲስ ጥረቶችን በዚህ ሣምንት አሳውቀዋል የተማሪዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ተግባራዊ የሆኑ የአውቶቡስ ኦፐሬተሮችን ለመቅጠር በብሔራዊ ደረጃ አዳጋች በሆነበት ወቅት ዲስትሪክቱ በጠዋት ወይም ከሰአት ፈረቃ ላይ ተጨማሪ መንገዶችን ለሚነዱ ለማናቸውም የአውቶቡስ ኦፕሬተሮች/የአሽከርካሪዎች የክፍያ ጥቅማ ጥቅም ወደነበረበት ይመልሳል፣ "መጓጓዣ ሳያገኙ ቀርተው የሚጠባበቁትን የሚያጓጉዝ አውቶቡስ" ያቀርባል በተለያዩ ምክንያቶች የአውቶቡስ መስመራቸው የተሠረዘባቸውን ማናቸውም በአውቶቡስ ፌርማታ የቀሩ ተማሪዎችን፣ እና የተሰረዙ የአውቶቡስ መስመሮች ወይም የዘገዩ የት/ቤት አውቶቡስ መስመሮች ማሳወቂያ የሚደርሳቸው አስተባባሪ ኦፊሰሮች ቦታዎችን በመቆጣጠር እና መጓጓዣን በማስተባበር ያግዛሉ። ሙሉውን መልእክት ያንብቡ
  1. busስለ ዲስትሪክቱ የበጀት አሠራር ሂደት ለማወቅ ቨርቹወል በሚካሄድ ውይይት ከእኛ ጋር ይሳተፉ
    MCPS ከሶስቱ የማህበረሰብ የበጀት መረጃ ልውውጥ ክፍለ ጊዜዎች ሁለተኛውን ሰኞ፣ ኖቬምበር 28 ያስተናግዳል። ይህ ለ 2024 የበጀት ዓመት ሱፐርኢንቴንደንት ዶ/ር ሞኒፋ ማክኒት ያቀረቡት የስራ ማስኬጃ በጀትን እንዴት ለመገንባት እንደታቀደ ለማወቅ እድል ይሰጣል። ስብሰባው የሚካሄደው ቨርቹወል 6፡30–8 p.m. ነው።
    በዙም (Zoom) ይቀላቀሉን
    ለመደወል ከፈለጉ/Dial-in Option: 3017158592
    የዌብናር ቁጥር/Webinar ID: 858 0599 3380
    የይለፍ ኮድ ቁጥር (Passcode)፦ 551492
  1. athletics logoበዊንተር ወቅት 2022-2023 ስለ MCPS የአትሌቲክስ ደህንነት እቅድ ይወቁ
    ይህ እቅድ ለትልቅ እና የቤት ውስጥ ዝግጅቶች ልዩ ሁኔታዎችን ግምት ውስጥ በማስገባት የመጀመሪያውን የአትሌቲክስ ደህንነት እቅድ ተገቢ ማሻሻያዎችን ይዟል። የዚህ ወቅት እቅድ የመመሪያ መርሆችን፣ መምሪያው ሊወስዳቸው የሚችላቸው እርምጃዎች እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱን መፍትሔ ይሰጣል። የዚህን አመት የደህንነት እቅድ ያንብቡ።
  1. athletics logo2023–2024 የትምህርት ቤት የቀን መቁጠሪያ ላይ የእርስዎን ሃሳብ/አስተያየት ይስጡ
    ከእርስዎ መስማት እንፈልጋለን! እባኮትን ስለቀጣዩ አመት የትምህርት ቤት የቀን መቁጠሪያ  (ካለንዳር) ሃሳብዎን ያካፍሉን። ይህ ፈጣን የዳሰሳ ጥናት ለ 2023-2024 የትምህርት ዘመን በተዘጋጁ የቀን መቁጠሪያ (ካለንዳር) ሁኔታዎች ላይ የማህበረሰቡን አስተያየት ለማወቅ ይረዳል። ማክሰኞ፥ ዲሰምበር 6 በትምህርት ቦርድ ስብሰባ ላይ የሚቀርበውን የመጨረሻ ምክረሃሳብ ለማዘጋጀት ሠራተኞች የእርስዎን ግብረ መልስ ይጠቀማሉ። ሐሳብዎን እስከ ረቡዕ፣ ኖቨምበር 30 ያካፍሉን። የዳሰሳ ጥናቱን ሠነድ እዚህ ያግኙ

  2. CPS ለወላጆች ስለ ESL ትምህርት ቨርቹወል ውይይቶችን ያስተናግዳል

    MCPS እንግሊዝኛ ሁለተኛ ቋንቋቸው ለሆኑ አዋቂዎች የእንግሊዝኛ ትምህርት ስለሚሊሰጥበት ሁኔታ ከሞንትጎመሪ ካውንቲ (LCMC) የሊተርሲ ካውንስል ጋር ተከታታይ ቨርቹወል ውይይቶች ያደርጋል። ውይይቶቹ በእንግሊዝኛ፣ በቻይንኛ እና በስፓኒሽኛ ቋንቋዎች ይስተናገዳሉ። LCMC እንግሊዘኛን እንደ ሁለተኛ ቋንቋ ለ MCPS ወላጆች እና አሳዳጊዎች በነጻ ይሰጣል። ለሁሉም ደረጃ የእንግሊዝኛ ተናጋሪዎች የቨርቹወል እና በአካል የመማር አማራጮች ይኖራሉ። እንግሊዝኛ የመጀመሪያ ቋንቋቸው ላልሆነ ወላጅ ሁሉ ይሰጣል። ስለ ESL ትምህርቶች የፍላጎት መግለጫ ቅጽ

  1. crossing guardsየማህበረሰባችንን ደህንነት ለመጠበቅ በማቋረጫ መንገዶች ላይ ጠባቂዎች ያስፈልጋሉ።
    የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፖሊስ መምሪያ ለመሻገሪያ/ማቋረጫ መንገድ ጠባቂዎች ክፍት ቦታዎች አሉት። ክፍት ቦታው የትምህርት ቤት ልጆችን እና ሌሎች እግረኞችን መንገድ እንዲያቋርጡ መርዳት እና በተመደቡ ማቋረጫዎች ላይ የትራፊክ ቁጥጥር ማድረግን ያካትታል። ስለ ሰዓት፣ ስለ ጥቅማጥቅሞች እና እንዴት ማመልከት እንደሚቻል ለማወቅ እዚህ ጠቅ ያድርጉ።
  1. athletics logoአስደሳች ዜና
    ፎል ወቅት ተማሪ አትሌቶቻችን ድል የተቀዳጁበት ጊዜ ነው
    የፑልስቪል ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ወንዶች የሀገር አቋራጭ ቡድን እና የደማስከስ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ቺርሊዲንግ ቡድን በሳምንቱ መጨረሻ 2A የስቴት ሻምፒዮና ዋንጫ አሸንፈዋል። MCPS ቺርሊዲንግ ሻምፒዮና አሸናፊ ለመሆን ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። እንዲሁም በሻምፒዮናው የፍጻሜ ውድድር ላለፉት ቡድኖች እንኳን ደስ አላችሁ! – የዊንስተን ቸርችል ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የወንዶች አገር አቋራጭ እና የሴቶች የሜዳ ሆኪ፣ የዋልተር ጆንሰን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የሴቶች አገር አቋራጭ፣ የፑልስቪል የሴቶች አገር አቋራጭ ቡድኖች ሲሆኑ፥ እንዲሁም የሼርዉድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቺርሊዲንግ ቡድን የሶስተኛነት ደረጃ አግኝተዋል። የዋልት ዊትማን (Walt Whitman) የወጣት ሴቶች እግር ኳስ ቡድን በ 5 p.m. ላይ ኩዊንስ ኦርቻርድ (Quince Orchard) ጋር ቅዳሜ ኖቬምበር 19 "Loyola University in the first-ever all-MCPS 4A state championship!! ይጫወታሉ።

    athletics logoየማርሽ ባንዶች በሪጅናል/ስቴት ሻምፒዮና ከፍተኛ ክብርን ተቀዳጅተዋል
    ቶማስ ኤስ ዎተን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (Thomas S. Wootton HS) የሜሪላንድ ማርቺንግ ባንድ ማህበር (MMBA) የዌስተርን ሪጅናል ሻምፒዮና በትንሽ-ክፍት ክፍል አሸናፊ ሆኗል፣ እንዲሁም ለምርጥ ከለር ጋርድ፣ ምርጥ አጠቃላይ ውጤት፣ ምርጥ የሙዚቃ አፈጻጸም እና ምርጥ የእይታ የአፈጻጸም ሽልማቶችን አግኝቷል። ኩዊንስ ኦርቻርድ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (Quince Orchard HS) Class 1A State Championship አሸንፏል፣ እንዲሁም ክላርክስበርግ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (Clarksburg HS) MMBA ስቴት ሻምፒዮና Class 3A ስቴት ሻምፒዮና አሸንፈዋል፣ ኖቬምበር 6፥ ኩዊንስ ኦርቻርድ (Quince Orchard) ምርጥ የሙዚቃ አፈጻጸም ሽልማትን ሲያገኝ ክላርክስበርግ/Clarksburg ምርጥ የፐርከስሽን ምርጥ ከለር ጋርድ፣ ምርጥ የእይታ አፈጻጸም፣ እና ምርጥ የአጠቃላይ ውጤት አሸናፊ ሆኗል። በዚህ አመት ለተወዳደሩት MCPS ማርሽ ባንዶች ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ!  ሞንትጎመሪ ብሌር (Montgomery Blair)፣ ክላርክስበርግ (Clarksburg)፣ ኩዊንስ ኦርቻርድ (Quince Orchard)፣ ሮክቪል (Rockville) እና ዉተን (Wootton)!
  1. ማሳሰቢያ፦ ኖቬምበር 23፣ 24፣ እና 25 ትምህርት ቤቶች እና ቢሮዎች ይዘጋሉ።
    እንዲሁም፣ ኖቬምበር 21-22 ተማሪዎች ቀደም ብሎ የሚለቀቁባቸው ቀናት መሆናቸውን አስታውሱ። የሐሙስ መታወቅ ያለባቸው ነገሮች ዲሴምበር 2 ይመለሳል። እስከዚያው ድረስ፣ የሚፈልጉትን መረጃ ለማግኘት ድረ ገጻችንን ይጎብኙ።
    ከባድ የአየር ሁኔታ በሚከሰትበት ወቅት ከ MCPS ጋር ግንኙነት ይኑርዎት
    MCPS ስለ ትምህርት ቤት መዘጋት፣ ስለሚዘገዩ ቦታዎች እና መጥፎ የአየር ሁኔታ ሲኖር ተማሪዎች በቅድሚያ ስለሚሰናበቱበት ሁኔታ ለማሳወቅ ብዙ መንገዶችን ይጠቀማል። ስለ አየር ሁኔታ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን እና ከ MCPS ጋር እንዴት መገናኘት እንደሚችሉ የበለጠ ለማወቅ፦  ግንኙነትዎን ይቀጥሉ የአደጋ ጊዜ መረጃን እንዴት እንደሚቀበሉ

የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ
Montgomery County Public Schools 



Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org

Montgomery County Public Schools