ቀጣዩስ ምንድነው፦

የድንበር ጥናት - ሀሳብዎን ይግለጹልን

ለተከበራችሁ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) ማህበረሰብ 

ስለ ቻርለስ W. ውድዋርድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደገና መከፈት፣ የክራውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መከፈት እና የደማስከስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መስፋፋት ላይ ያተኮረ የድንበር ጥናት ተሳትፎ ክፍለ ጊዜዎች ላይ የተገኙትን ሁሉ እናመሰግናለን። እነዚህን ተጨማሪ አዳዲስ ቦታዎችን ማስፋት ማለት ዲስትሪክቱ በርካታ የትምህርት ቤት ድንበሮችን ማዘመን/ማሻሻል ያስፈልገዋል ማለት ነው። እነዚህ ለውጦች መደረግ ያለባቸው አዲሶቹን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተመጣጣኝ ተማሪዎች እንዲኖራቸው ያደርጋሉ፣ አሁን ባሉት የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ያለውን የተማሪዎች መጨናነቅ ያቃልላሉ፣ እና በወሰን ጥናት ውስጥ በተካተቱት የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች እና መለስተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የተሻለ ሚዛናዊ የተማሪዎች ምዝገባ ስለሚኖር — ሁሉም ተማሪዎች የተቻለውን ያክል ተመጣጣኝና ፍትኃዊ የመማር ልምድ እንዲያገኙ ይደረጋል።

በተሳትፎ ክፍለ ጊዜዎቹ ስለ 2027-2028 የትምህርት አመት የታቀዱ የትምህርት ቤት ድንበሮችን በቅድሚያ እንዲያውቁ ግንዛቤ ተሰጥቷል። በእነዚህ ክፍለ-ጊዜዎች ላይ የመጨረሻው የድንበሮች ውሳኔ እንዳልቀረበ ማወቅ አስፈላጊ ነው፤ በዚህ ሂደት ውስጥ የቀረቡት አማራጮች የመጀመሪያው እርምጃ ነው። የድንበር ጥናት ሂደት የሚመራው በቦርድ ፖሊሲ FAA መሠረት በትምህርት ተቋማት እቅድ ነው። ስለ ድንበር ጥናት አማራጭ ምክረሃሳቦች ሲዘጋጁ በዚህ የቦርድ ፖሊሲ ውስጥ የተዘረዘሩት አራት ምክንያቶች ግምት ውስጥ ይገባሉ። እነዚህ አራት ምክንያቶች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦

  • የተማሪ ማህበረሰብ ስብጥር ባህርያት

  • ጂኦግራፊ

  • የትምህርት ቤት ምደባዎች የሚቆዩበት ጊዜ

  • የፋሲሊቲ አጠቃቀም

እነዚህ ስለ ትምህርት ቤት ድንበሮች የሚደረጉ ውይይቶች በብዙ ቤተሰቦች ላይ ተጽእኖ ሊኖራቸው ይችላል። ለዚህም ነው ይህ ሂደት የማህበረሰብን ተሳትፎ ማካተት ያለበት። በጥንቃቄ የታሰበበት፣ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን እንድናደርግ እንዲያግዘን የእርስዎ አስተያየት አስፈላጊ—ስለሆነ ከእርስዎ መስማት እንፈልጋለን። በዚህ የበልግ ወቅት (ፎል)፣ በዚህ የማጣሪያ ውይይት ወቅት በሚቀርቡት አማራጮች ላይ ተጨማሪ ግብረመልስ ማግኘት የሚያስፈልገን ክለሳ የተደረገባቸው የድንበር አማራጮች ይቀርባሉ። 

እባክዎን ሀሳብዎን ለማጋራት ይህንን የዳሰሳ ጥናት ሞልተው ይመልሱ (ውድዋርድ/Woodwardክራወን እና ደማስከስ/Crown and Damascus

የሚደረጉት ለውጦች የእርስዎን ተማሪ እንዴት ሊነኩ እንደሚችሉ አሁንም ጥያቄ ወይም ስጋት ሊኖርዎት እንደሚችል እናውቃለን። እናበረታታዎታለን፦

ከእርስዎ የምናገኘው ግብአት አስፈላጊ ነው። አለበለዚያ ቁልፍ የሆኑ አስተያየቶች ሊቀሩብን ይችላሉ። የማህበረሰባችን ንቁ ​​ተሳታፊ ስለሆኑ እና የትምህርት ቤቶቻችንን የወደፊት ዕጣ ፈንታ ለማስተካከል ስለሚያደርጉት ትብብር እናመሰግናለን.


በዚህ አድራሻ ኢሜል ያድርጉልን፦ ASKMCPS@mcpsmd.org