አበይት ጉዳዮች

የትምህርት ቦርድ ወቅታዊ መረጃዎች
ጁን 5, 2026

የሞንትጎመሪ ካውንቲ የትምህርት ቦርድ ጁን 4 ባካሄደው የሥራ ክፍለ ጊዜ ለበጀት ዓመት 2027 የሥራ ማስኬጃ በጀት $3.72 ቢሊዮን ዶላር አጽድቋል። ቦርዱ የሪጅናል የፋይናንስ ጫናዎችን በመጋፈጥ፣ የአሠራር እውነታዎችን እና የትምሕርት አሰጣጥን ለማስቀጠል ያለውን ጥልቅ ቁርጠኝነት በማመጣጠን ባሳለፈው የመጨረሻ የበጀት ውሳኔ $36 ሚሊዮን ዶላር ክፍተት በማቻቻል ወስኗል። በአስቸጋሪ የበጀት ቅነሳ ሁኔታዎች፣ በጀቱ ዋና ዋና የአካዳሚክ ፕሮግራሞችን ለማካሄድ/ለማስቀጠል እና የትምህርት ቤቶችን የሥነ ልቦና ባለሙያዎች እና የኮሌጅ ናቪጌተሮችን ጨምሮ በቀጥታ ለተማሪዎች አስፈላጊ የሆኑ ጉዳዮችን ያከናውናል። ከፋይናንስ እቅድ ባሻገር፣ ቦርዱ የሶስተኛ ሩብ ዓመት የአካዳሚክ አፈፃፀምን ገምግሟል፣ እየተሻሻለ የመጣውን MCPS አትሌቲክስ ገጽታ ተወያይቷል፣ ለቀጣዩ የትምህርት ዓመት "Leveling Up" ስልቶችን ዘርዝሯል፣ እንዲሁም የተማሪዎችን የስክሪን አጠቃቀም ጊዜ እና የማህበረሰብ ተሳትፎን በተመለከተ አዲስ የአሠራር ሁኔታን አስተዋውቋል።


የበጀት አመት FY 2027 አጠቃላይ በጀት | የሦስተኛ ሩብ ዓመት Q3 አካደሚክ አፈጻጸም | MCPS አትሌቲክስ & ታይትል IX | ከፍተኛ ደረጃ ለማደግ ማሻሻል | አዲስ ቢዝነስ


የበጀት ዓመት 2027 የሥራ ማስኬጃ በጀት የማፅደቅ ውሳኔ

ቦርዱ ለሞንትጎሞሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) የበጀት ዓመት 2027 $3.72 ቢሊዮን ዶላር የሥራ ማስኬጃ በጀት አጽድቋል። ዲስትሪክቱ ካቀረበው የመጀመሪያ ጥያቄ $36 ሚሊዮን ዶላር እጥረት ቢኖርበትም፣ መጨረሻው የፀደቀው በጀት የክፍል ትምህርትን ባለበት ደረጃ ለመቀጠል፣ ወሳኝ የተማሪዎችን ድጋፍ ለመጠበቅ እና በተቻለ መጠን የቅነሳ ተጽእኖን ለመገደብ ቅድሚያ ተሰጥቷል።

የበጀት ቅነሳው 415 የሥራ መደቦች ላይ ተጽዕኖ ቢኖረውም፣ በአሁኑ ጊዜ 159ቱ ክፍት ናቸው፣ ስለዚህ ተጽዕኖ የሚደርስባቸው ሠራተኞች ያለፍላጎት በሚደረገው የዝውውር ሂደት ወደ ሌሎች የሥራ መደቦች ሊመደቡ ይችላሉ። የዲስትሪክቱ መሪዎች የዲስትሪክቱን ዋና ተልዕኮ ማለትም የማስተማርን ዋና ተልእኮ ​​በመጠበቅ የረጅም ጊዜ የፋይናንስና በጀት መረጋጋትን ለማስጠበቅ አስቸጋሪ ውሳኔዎችን ማድረግ አስፈላጊ መሆናቸውን አፅንዖት ሰጥተዋል።

ዋና ዋና የሥራ መዋቅሮችን መጠበቅ በተመለከተ፡ የተፀደቀው በጀት በተማሪዎች የስነ አእምሮ ጤና እና የማስተማር ዘርፎች ላይ ኢንቨስትመንቶችን በመቀጠል የትምህርት ቤት የሥነ ልቦና ባለሙያዎችን፣ የትምህርት ድጋፍ ሰራተኞችን፣ የኮሌጅ እና የሙያ ዝግጁነት ሥራ መደቦችን እና የትምህርት ቤት ደህንነት የሥራ መደቦችን ጨምሮ ቁልፍ ድጋፎችን ይጠብቃል።

ሙሉውን የበጀት ዝርዝሮችን ውሳኔ ያንብቡ

ጁን 4 የቦርድ ስብሰባ እና የበጀት ውሳኔ አሰጣጥ ይመልከቱ


የትምህርት ዓመት 2025–2026 የትምህርት አፈፃፀም (ሦስተኛ ሩብ ዓመት)

ቦርዱ የሶስተኛ ሩብ ዓመት የትምህርት አፈጻጸም መረጃ ገምግሟል፣ ይህም የትምህርት ዓመቱ ሊጠናቀቅ እየተቃረበ ሲሄድ ወሳኝ መለኪያዎችን ያንፀባረቀ ነው።

ይህ ወቅታዊ መረጃ በመካከለኛ እና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሊተርሲ ትምህርት (literacy) እድገት፣ በአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሂሳብ ትምህርት መሻሻል እና ጠንካራ የኮርስ አፈጻጸም መኖሩን ያመለክታል። በተቃራኒው፣ MCPS የተማሪዎችን የአፈጻጸም መረጃ በመጠቀም የትምህርት አሰጣጥን ለማጠናከር እና የትምህርት እድሎችን ክፍተቶች ለመዝጋት 6ኛ ክፍል የሂሳብ ትምሕርት ትኩረት የሚሰጠው የድጋፍ ዘርፍ ሆኖ ይቀጥላል።

SY 2025–2026 የትምህርት አፈፃፀም፡ የሶስተኛ ሩብ ዓመት ሪፖርት ያንብቡ


MCPS አትሌቲክስ ወቅታዊ መረጃ፡ታይትል IX ማስፋፋት እና የጂምናስቲክስ የወደፊት ዕጣ ፈንታ

ቦርዱ ስለ MCPS አትሌቲክስ ወቅታዊ መረጃ አግኝቷል፣ ይህም የተማሪዎችን ተሳትፎ፣ ታይትል Title IX ቀጣይነት እና STUNT እና የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስግኔቸር እግር ኳስን ጨምሮ የአትሌቲክስ እድሎችን ለማስፋት የታቀደ ነው።

ሰራተኞቹ የጂምናስቲክን እንቅስቃሴ ማቆምን በተመለከተ የቀረበውን ምክረ ሀሳብ ጭምር ገምግመዋል፤ ይህም የተሳትፎ መቀነስ፣ የአሰልጣኞች እጥረት እና የረጅም ጊዜ የዘላቂነት ስጋቶችን የሚጠቅስ ነው።

ይህ ለቤተሰቦች ምን ማለት ነው፡ MCPS የወደፊት የፕሮግራም አቅርቦቶችን ሲገመግም እና በዲስትሪክቱ ውስጥ ፍትሃዊ የአትሌቲክስ እድሎችን ለማመቻቸት እየሰራ ስለሆነ ጂምናስቲክን ጨምሮ የአትሌቲክስ ፕሮግራሞች 2026–2027 የትምህርት አመት ላይ ይቀጥላሉ።

ጁን 4 የቀረበውን የአትሌቲክስ ወቅታዊ መረጃ ይመልከቱ


2026-2027 እና ከዚያም በላይ ደረጃን ማሻሻል

የሞንትጎሞሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) መሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት የታቀዱ ቁልፍ ተነሳሽነቶችን አጠቃላይ አቅጣጫ አቅርበዋል፤ ይህም የትምህርት ልህቀትን እና የአሠራር ማሻሻያዎችን ለማምጣት የታለመ ነው። ክለሳዎቹ እና ማሻሻያዎቹ ይበልጥ የሚያተኩሩት፦

  • የትምሕርት ውጤት አሰጣጥ ላይ፦ ወጥነት እንዲኖረው ለማድረግ በስርዓት አቀፍ ደረጃ የግምገማ መስፈርቶችን ማሻሻል/ማስተካከል።
  • የተማሪዎች የድጋፍ አገልግሎቶች፦ የአእምሮ ጤና እና የአካዳሚክ ድጋፍ ማዕቀፎችን ማስፋፋት።
  • የትምህርት ቤት የደህንነት ጥበቃ እርምጃዎች፦ በትምህርት ቤት ግቢዎች ውስጥ የደህንነት አጠባበቅን ማጠናከር።
  • የሞባይል ስልክ አጠቃቀም ፖሊሲ፦ የክፍል ውስጥ ትኩረትን የሚያደናቅፉ ነገሮችን ለማስወገድ የተዘጋጀውን አዲስ ስርዓት አቀፍ ፖሊሲ መተግበር።

የቀረበው ምክረ ሃሳብ የአካዳሚክ ውጤቶችን፣ የአሠራር ቅልጥፍናን፣ እና የቤተሰብ ተሳትፎን ለማሻሻል የረጅም ጊዜ ጥረቶችን እንደ ወደፊት ስትራቴጂክ ዕቅድ አካል አድርጎ ዘርዝሯል።

ስለወደ ቀጣይ ደረጃ ማሻሻል የቀረበውን ያንብቡ


አዲስ ቢዝነስ ላይ ይሳተፉ

ከመዋእለ ህጻናት እስከ ስምንተኛ ክፍል (K-8) የተማሪዎችን የስክሪን አጠቃቀም ሰዓት ኦዲት ማድረግ

የቦርድ አባል ጁሊ ያንግ/Julie Yang ለአንደኛ እና ለመካከለኛ ደረጃ ተማሪዎች የዲጂታል መሳሪያዎችን አጠቃቀም አጠቃላይ ግምገማ የሚመለከት አዲስ የውሳኔ ሀሳብ አስተዋውቀዋል። ለመጀመሪያው የቦርድ ግምገማ እና ለወደፊት እርምጃ የቀረበው የውሳኔ ሀሳብ፦ የተማሪዎችን ትኩረት፣ እንቅልፍ፣ እና አካላዊ ጤንነት ለመጠበቅ ዘመናዊ የዲጂታል መሳሪያዎችን ከተለምዶአዊ የማስተማሪያ ዘዴዎች ጋር ማመጣጠን አስፈላጊ መሆኑን ያንፀባርቃል።

የውሳኔ ሀሳቡ ወደፊት በሚደረግ የድምጽ አሰጣጥ ከፀደቀ፣ MCPS እስከ ማርች 2027 ድረስ ለቦርዱ መደበኛ የግምገማ ሪፖርት እንዲያቀርብ ይመራዋል።

  • ዕለታዊ አጠቃቀምን መለካት፦ ከመዋእለ ህጻናት እስከ ስምንተኛ ክፍል (K-8) ተማሪዎች አማካይ የዕለታዊ እና የሳምንታዊ የትምህርት ቀን የስክሪን አጠቃቀም ጊዜን መለካት፣ የማስተማሪያ እና በትምህርት ላይ በማይሆኑበት ጊዜ መካከል ያለውን የ አጠቃቀም ልዩነት መለካት ነው።
  • የተቀነሰውን ያህል ጊዜ መለየት፦ በትምህርት ቀን ውስጥ ስክሪን ለማየት ተጋልጠው የሚቆዩበትን ጊዜ ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ ለመቀነስ ከእድሜ ጋር የሚስማሙ ሁኔታዎችን መገምገም ያስፈልጋል።
  • የይዘት ማጣሪያዎችን ይገምግሙ፦ ተማሪዎች በትምህርት ቤት በተሰጡ መሳሪያዎች ላይ ጎጂ ወይም ተገቢ ያልሆኑ ነገሮችን መመልከት እንዳይችሉ ለማረጋገጥ የዲስትሪክቱን የደህንነት ማጣሪያ ውጤታማነት ይገምግሙ።
  • ዲስትሪክት አቀፍ መመሪያዎችን መመልከት፦ ግልጽ፣ ለዕድሜ ተስማሚ የሆኑ ስክሪን የማያ ጊዜ ገደቦችን ያቅርቡ፣ እንዲሁም ማንኛውንም መዋቅራዊ ለውጦች የአሠራር ተፅእኖዎችን ይግለጹ።

ስለ መዋእለ ህጻናት እስከ ስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች (K-8) ስክሪን የማያ ገጽ ጊዜ ውሳኔ ሰነድ ያንብቡ

የኮሙኒኬሽን እና የማህበረሰብ ተሳትፎ አማካሪ ኮሚቴ አባልነት

ቦርዱ ከጁላይ 1, 2026 እስከ ጁን 30, 2027 ድረስ ለሚቆየው የኮሙኒኬሽን እና የማህበረሰብ ተሳትፎ አማካሪ ኮሚቴ አዲስ አባላት እንዲሾም የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ አጽድቋል።

ኮሚቴው MCPS እና ቦርዱ ወሳኝ በሆኑ የዲስትሪክት ተነሳሽነቶች ላይ ከቤተሰቦች ጋር እንዴት መገናኘት እንዳለባቸው በጥራት የማካሄድ ኃላፊነት አለበት። ለቀጣዩ የትምህርት አመት፣ ዋና ትኩረታቸው በመጪው የአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች የወሰን ጥናት ዙሪያ ላይ ያተኮረ ሁሉን አቀፍ የግንኙነት እቅድ ማዘጋጀት እና ተግባራዊ ማድረግ ይሆናል።

ስለ አማካሪ ኮሚቴ የውሳኔ ሰነድ ያንብቡ


ቀጣይ ስብሰባዎች

ሐሙስ፣ ጁን 25 የቦርድ መደበኛ ስብሰባ (ከሰዓት በኋላ 4፡00 p.m.)
ማክሰኞ፣ ጁን 30 የፖሊሲ አስተዳደር ኮሚቴ (ከሰዓት በኋላ 3፡00 p.m.)
ሰኞ፣ ጁላይ 6ተማሪ የቦርድ አባል/SMOB የቃለ መሃላ ሥነ ሥርዓት ይከናወናል (4፡00 p.m.)


ከእኛ ጋር ያለዎትን ግንኙነት ይቀጥሉ

በህዝባዊ የውይይት መድረኮች ላይ አስተያየት ለመስጠት ይሳተፉ። 

FacebookInstagramBluesky፣ እና X ላይ ይከታተሉን

ኢሜል ይላኩልን፦ boe@mcpsmd.org


ኢሜል ይላኩልን፦ boe@mcpsmd.org