የሞንትጎመሪ ካውንቲ የትምህርት ቦርድ ሜይ 21 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የመጪውን የትምህርት አመት የሚመለከት ከባድ አጀንዳ ተመልክቷል፣ ይህም $36 ሚሊዮን ዶላር የበጀት ክፍተት መፍትሄዎችን እና ጊዜያዊ የበጎ ፈቃድ ሰራተኞች ጉዳይ፣ እና ጡረታ መውጣትን የማበረታታት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ቦርዱ በተማሪዎች የምግብ ዋጋ ላይ ማስተካከያ እንዲደረግ የቀረበለትን አጀንዳ አጽድቋል፤ እንዲሁም በክፍል ውስጥ ለትምህርት ቴክኖሎጂ እና ለአእምሮ ህክምና አገልግሎት ወሳኝ የሆኑ አዳዲስ የመከላከያ መንገዶችን በሚመለከት የመጨረሻ ውሳኔ አሳልፏል።
ቦርዱ በዚህ ስብሰባ ላይ የኤዥያ አሜሪካውያን የፓስፊክ ደሴት ነዋሪዎችን ቅርስ የሚዘከርበት ወር፣ አይሁድ አሜሪካውያንን ቅርስ የሚዘከርበት ወር፣ የመምህራን አድናቆት ሳምንት፣ እና የተማሪ ሰራተኞች ሳምንትን በማክበር እንዲሁም 2026 የትምህርት ቤት ካውንስለሮች የአመቱን ምርጥ ካውንስለር እውቅና በመስጠት አክብሯል።
ስለ FY 2027 ባጀት | ክፍት የምሳ ጊዜ | ስለ ትምህርት ቴክኖሎጂ አጠቃቀም | ፖሊሲ መቅረጽ | የምግብ ዋጋ | ክብረ በዓላትየመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
ቦርዱ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ካውንስል ያደረገውን የመጨረሻ የባጀት ድልድል ተከትሎ የተፈጠረውን $36 ሚሊዮን ዶላር የበጀት ክፍተት ለመዝጋት የሚያስፈልጉትን መዋቅራዊ ማስተካከያዎች ገምግሟል።
ቦርዱ አስፈላጊ የሆኑ ቅነሳዎች በትምሕርት ዘርፎች ላይ ተጽእኖ በማይፈጥርበት ሁኔታ በተቻለ መጠን ጥንቃቄ እንዲደረግ ለማድረግ እየሰራ ነው።
ይህንን የባጀት እጥረት ለመቅረፍ እና የተማሪዎችን የምዝገባ ዝውውር ለማካሄድ፣ MCPS ጡረታ ለመውጣት ብቁ ለሆኑ ሠራተኞች በፈቃደኝነት የጡረታ ማበረታቻ እያቀረበ ነው። ይህ ስትራቴጂ 27ኛው የበጀት ዓመት እና 28ኛው የበጀት ዓመት ላይ የአሠራር ወጪ ቁጠባን ከፍ ለማድረግ የተነደፈ ሲሆን፣ በበጀት ቅነሳ ምክንያት ሊፈናቀሉ ለሚችሉ ሌሎች ሰራተኞች ቦታዎችን ክፍት ለማድረግ የተነደፈ ነው።
ቀጣይ እርምጃዎች፡ ቦርዱ ጁን 4 በሚያደርገው ስብሰባ ላይ ስለ በጀት ዓመት 2027 የሥራ ማስኬጃ በጀት ላይ የመጨረሻ እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ሁሉንም ግብረመልሶች እና ከአስተዳደሩ የሚቀርቡትን ሀሳቦች ይገመግማል።
ሜይ 21 የቦርድ ስብሰባ እና የበጀት ውይይት ላይ ይመልከቱ
ቦርዱ ስለ ፖሊሲ JEF (ክፍት የምሳ ጊዜ ፖሊሲ) ላይ የቀረቡትን ለውጦች ተወያይቷል። ቦርዱ ፖሊሲውን ለመሻር እና ክፍት የምሳ ጊዜ እንዲሆን ለማድረግ ክትትል መደረግ ያለበት በሱፐርኢንቴንደንቱ ውሳኔ እንዲሆን የፖሊሲ አስተዳደር ኮሚቴ የሰጠውን ሀሳብ ግምት ውስጥ አስገብቷል። ሆኖም ግን፣ ይህ ሀሳብ ሕዝብ አስተያየት እንዲሰጥበት የቀረበው ሀሳብ ሊጸድቅ አልቻለም።
የፖሊሲውን ቋንቋ ለማሻሻል ኮሚቴው ያቀረበው ሀሳብም አልተወሰነም። በዚህ ምክንያት ቦርዱ ምንም አይነት እርምጃ ስላልወሰደ ፖሊሲው እንዳለ ሳይለወጥ ቆይቷል።
ይህ ለቤተሰቦች ምን ማለት ነው፡
ለወራት የህዝብ አስተያየት እና የኮሚቴ ግምገማ ከተደረገ በኋላ፣ ቦርዱ ፖሊሲ IGS (የትምህርት ቴክኖሎጂ)ማሻሻያዎችን ለማፅደቅ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጥቷል።
የተሻሻለው ፖሊሲ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በክፍል ውስጥ ደህንነቱ በተጠበቀ እና ኃላፊነት በተሞላበት ሁኔታ እንዴት ጥቅም ላይ ሊውሉ እንደሚችሉ ግልጽ፣ ዲስትሪክት አቀፍ መመሪያዎችን አስቀምጧል። ክለሳዎቹ በአብዛኛው የሚያተኩሩት በሚከተሉት ላይ ነው፦
ቀጣይ እርምጃዎች፦ MCPS ወደ መማሪያ ክፍሎች ከማስገባቱ በፊት AI መሳሪያዎችን ያጣራል፤ እና ኃላፊነት የተሞላበት AI አጠቃቀም ላይ ያተኮረ እና AI የሚመነጭ የተሳሳተ መረጃን በመለየት ላይ ያተኮረ የሰራተኞች ስልጠና ያዘጋጃል።
ቦርዱ የዲስትሪክት ፖሊሲዎች እንዴት እንደሚዘጋጁ፣ እንደሚገመገሙ፣ እና እንደሚሻሻሉ የሚቆጣጠርበትን ፖሊሲ BFA ማሻሻያዎችን አጽድቋል።
እነዚህ ለውጦች የፖሊሲ አወጣጥ ሂደቱን ለቤተሰቦች የበለጠ ግልጽ እና ተደራሽ ለማድረግ የታለሙ ናቸው። የተደረጉት ክለሳዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦
እየጨመረ የመጣውን የምግብ፣ የሰው ኃይል እና የሥራ ወጪን ለማመጣጠን፣ ቦርዱ የበጀት ዓመት 2027 የተማሪዎች ቁርስ እና ምሳ ዋጋ ላይ $0.30 ጭማሪ አጽድቋል።
የዲስትሪክቱ ባለስልጣናት ይህ ማስተካከያ የትምህርት ቤቶችን የአመጋገብ ፕሮግራም የፋይናንስ መረጋጋት ለመጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን እና ጥብቅ የፌዴራል የአመጋገብ ደረጃዎችን የሚያሟሉ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የተማሪዎች ምግቦችን ለማቅረብ በምግብ ዋጋ ላይ ማሻሻያ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
ሜይ 21 የቦርድ ስብሰባ እና የምግብ ዋጋ ማስተካከያ ውሳኔን ይመልከቱ
በዚህ ሜይ ወር፣ ቦርዱ በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የኤዥያ አሜሪካውያን፣ የሃዋይ ተወላጆች እና የፓስፊክ ደሴት ነዋሪዎች የዳበረ ታሪክ፣ ባህል፣ እና ስኬቶችን ለማክበር እና ለመዘከር የኤዥያ አሜሪካውያን እና የፓስፊክ ደሴት ነዋሪዎች የቅርስ ወር በማክበሩ ኩራት ይሰማዋል። AAPI ማህበረሰብ አስተዋፅዖዎች አስፈላጊ ናቸው፣ የአገራችንም ታሪክ ያለእነሱ የተሟላ አይደለም። የቦርድ አባል ጁሊ ያንግ/Julie Yang ከሊግ ኦፍ ኤጁኬተርስ ፎር ኤዥያን አሜሪካን ፕሮግረስ "League of Educators for Asian American Progress" የተውጣጡ ተወካዮችን፣ የኤዥያን አሜሪካን የጤና ጥበቃ ተነሳሽነት ዋና ዳይሬክተርን እና የካልካታ ዩኒቨርሲቲ አስተማሪዎችን እውቅና ሰጥተዋቸዋል። በተጨማሪም፣ ቦርዱ LEEEAP ስኮላርሺፕ ተቀባዮች ለሆኑት ተማሪዎች Jonathan Ta, Chloe Kim እና Raven Miralles እንዲሁም የዳርነስታወን አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር Darshan Jain እውቅና ሰጥቷል። ለኤዥያን አሜሪካውያን ያለፈውን፣ የአሁኑን፣ እና የወደፊቱን በሚያስደንቅ ሁኔታ የሚያንፀባርቁትን ስለትጋታችሁ እና ስለስኬታችሁ ሁላችሁንም እናመሰግናለን።
ሜይ የአይሁዳውያን አሜሪካውያን ቅርስ የሚከበርበት ወቅት ሲሆን፣ በአገራችን ታሪክ ውስጥ የአይሁዳውያን አሜሪካውያንን ሰፊና የተለያዩ አስተዋጽኦዎች በመከበር ላይ ይገኛል። ዩናይትድ ስቴትስ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ እና ከዚያም በፊት፣ አይሁዳውያን አሜሪካውያን በሲቪክ ሕይወት ውስጥ እጅግ ጠቃሚ ሚና ተጫውተዋል፤ ከእነዚህም ውስጥ መንግስት፣ ትምህርት፣ ሳይንስ፣ ንግድ፣ ስነጥበብ እና የማህበረሰብ አገልግሎቶች ይገኙበታል። የቦርድ አባል ላውራ ስቱዋርት/Laura Stewart በስብሰባው ላይ የአይሁድ ማህበረሰብ ግንኙነት ምክር ቤትን፣ የሞንትጎመሪ ካውንቲ የአይሁድ አስተማሪዎች አለያንስን፣ የአይሁድ ማህበራዊ አገልግሎት ኤጀንሲን እና ቴምፕል ቤዝ አሚ እውቅና በመስጠት በሞንትጎመሪ ካውንቲ እና በአጠቃላይ በአገሪቱ ውስጥ የማይጠፋ እና ወሳኝ አሻራ ማኖራቸውን በጉልህ አንፀባርቀዋል።
በዚህ ዓመት፣ ብሔራዊ የህፃናት ማሰልጠኛ ማዕከል (PTA) ለብሔራዊ የመምህራን አድናቆት ሳምንት "ማጂክ" የተሰኘ ጭብጥ መርጧል። መምህራን ከተማሪዎቻቸውና ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር በየቀኑ የሚያካፍሉት ያለመታከት ቁርጠኝነት፣ አገልግሎት፣ እና ተነሳሽነት ልብንና አእምሮን ያስደንቃል፤ ይህ ከአስማት በስተቀር ሌላ ምን ይባላል? በማለት ገልጸውታል። የቦርድ አባል ናታሊ ዚመርማን/Natalie Zimmerman የሮሊንግ ቴራስ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቻርለስ ሲልበርማን፣ የሚል ክሪክ ታወን አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሰርጂዮ ካበሬራ እና MCEA ፕሬዝዳንት ዴቪድ ስታይን እና ምክትል ፕሬዝዳንት ዳኒሊያ ዊልሰንን እውቅና ሰጥተዋል። ምንም እንኳን በቦታው መገኘት ባይችሉም፣ ቦርዱ የግሬት ሴኔካ ክሪክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጁሊ ሊፕስማን፣ የዊተን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዣኔት ክሩዝ እና የኖርዝዉድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዳንኤል ስታይንንም እውቅና ሰጥቷል። የትምህርት ቦርዱ መምህራኖቻችን የሚቀጥለውን ትውልድ ተማሪዎችን በመምራት እና ለቀጣይ ስኬት ስላዘጋጁላቸው በጣም ያመሰግናቸዋል።
የቦርዱ ፕሬዝዳንት ግሬስ ሪቬራ-ኦቨን/Grace Rivera-Oven ሜይ 11–15 በዋለ ሳምንት MCPS ተማሪ የሰው ኃይል ሠራተኛ (PPW) ሳምንት እንዲሆን እውቅና ሰጥተዋል። የተማሪ ሰራተኞች MCPS በየቀኑ ሥራውም እንዲያንቀሳቅስ የሚያደርጉ ዋና አካል ናቸው፤ ቤተሰቦች የመገኘት ተግዳሮቶችን፣ የምግብ ዋስትና ማጣትን፣ በቤት ውስጥ የሚፈጠር አለመረጋጋትን፣ እና የአእምሮ ጤና ፍላጎቶችን እንዲያካክሱ የሚያግዙ በግንባር ቀደምትነት ያሉ ቁርጠኛ አስተማሪዎች ናቸው። በትምህርት ዓመቱ እና ከዚያም በኋላ የተማሪዎቻችንን እና የቤተሰቦቻችንን ሕይወት ለማሻሻል የሚሰሩትን እያንዳንዱን PPW አባላት በጥልቅ እንወዳቸዋለን።
ቦርዱ 2026 የዓመቱን ምርጥ የትምህርት ቤት ካውንስለሮችን በማክበር እውቅና በመስጠቱ ኩራት ይሰማዋል፤ እነርሱም ላውረን ሞርላንድ ከቤተዝዳ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ላቲሻ ኔልሰን ከሌክላንድስ መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና ስቴፋኒ ፓውል ከዊተን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ናቸው። ለማቀንቀን ያላቸው ድፍረት እና ለአገልግሎት ያላቸው ቁርጠኝነት MCPS ተማሪዎችን ለወደፊቱ የሚያዘጋጃቸው ብቻ ሳይሆን በዚህም ወቅት የትምህርት ቤቶቻችንን አገልግሎት የተሻለ አድርገውታል። ይህ እውቅና የመስጠት ሥነ ስርአት የትምህርት ቦርዱ የፍትሃዊነት ዋና እሴትን የሚያንፀባርቅበት ሲሆን እያንዳንዱ ተማሪ፣ ምንም አይነት ዳራ ሳይለይ፣ የራሱን ጉዞ ለመምራት የሚያስችለው መመሪያ፣ የአእምሮ ጤና ድጋፍ እና የአካዳሚክ መበረታታት እንዲኖረው ለማድረግ ያለማቋረጥ የሚሠሩ ቁርጠኛ አስተማሪዎችን ያከብራል።
ማክሰኞ፣ ሜይ 26 የስትራቴጂክ እቅድ ኮሚቴ (12:00 p.m.)
ሐሙስ፣ ጁን 4 የቦርድ የስራ ክፍለ ጊዜ (12:00 p.m.)
ሐሙስ፣ ጁን 25 የቦርድ መደበኛ ስብሰባ (ከሰዓት በኋላ 4፡00 p.m.)
ማክሰኞ፣ ጁን 30 የፖሊሲ አስተዳደር ኮሚቴ (ከሰዓት በኋላ 3፡00 p.m.)
በህዝባዊ የውይይት መድረኮች ላይ አስተያየት ለመስጠት ይሳተፉ።
Facebook፣ Instagram፣ Bluesky፣ እና X ላይ ይከታተሉን
ኢሜል ይላኩልን፦ boe@mcpsmd.org
ኢሜል ይላኩልን፦ boe@mcpsmd.org