የተከበራችሁ የ MCPS ማህበረሰብ፦
ዛሬ፣ ስለ ጤንነት/ደህንነት እና በመማር ማስተማር ላይ ባለን ቁርጠኝነት የመተንፈሻ አካላት በሽታዎች ሊያስከትሉ የሚችሉትን ተፅእኖዎች በመቀነስ ረገድ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስን (MCPS) ጥረት አጋራችኋለሁ። እነዚህ ጥረቶች የሚያተኩሩት የመተንፈሻ አካላት ላይ የሚተላለፍ ቫይረስ ስርጭትን በመቀነስ፣የኮቪድ-19 ስርጭትን በመቆጣጠር በትምህርት ቤቶች ውስጥ ስርጭትን ለመቀነስ እና የትምህርት ማቋረጥን በመቀነስ ላይ ነው። የማህበረሰባችንን የጤና አጠባበቅ አዝማሚያዎችን ለመከታተል እና ለህብረተሰባችን ግብዓቶችን እና ድጋፍ ለመስጠት ከሞንትጎመሪ ካውንቲ የጤና ጥበቃ እና ሰብአዊ አገልግሎት ዲፓርትመንት (DHHS) ጋር በቅርበት መስራታችንን እንቀጥላለን።
የአሁኑ ክረምት በህብረተሰብ ጤና ላይ አዳዲስ ፈተና ይዞ መጥቷል። ኮቪድ አሁንም ከእኛ ጋር አለ፣ በመከላከል እና በህክምና ብዙ መሻሻሎች ቢኖሩም፣ እንደ ኢንፍሉዌንዛ እና የመተንፈሻ አካል በሽታ RSV የመሣሰሉ ሌሎች ቫይረሶች በአካባቢያችን እና በክልላችን ላይ የተደራረበ የጤና ችግር እየፈጠሩ ናቸው።
በት/ቤቶች ውስጥ የመተንፈሻ አካላት በሽታ ስርጭትን መቀነስ
የኮቪድ-19 ስርጭት እና ተጋላጭነትን መቆጣጠር
በትምህርት ቤቶቻችን ውስጥ የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመቀነስ ምርመራ ማድረግ ወሳኝ መንገድ ነው።
በትምህርት ቀን ሊሆኑ የሚችሉ የኮቪድ-19 ምልክቶችን የሚያሳዩ ተማሪዎችን ምርመራ ማድረጋችንን እንቀጥላለን፣ እና DHHS ጋር በኮቪድ-19 ምርመራ እና ወረርሽኙ እንዳይስፋፋ የመግታት አጋርነታችንን እንቀጥላለን። DHHS ነፃ የኮቪድ-19 የክትባት ክሊኒኮችን እና የሞንትጎመሪ ካውንቲ ነዋሪዎችን ይመረምራል፤ ነፃ የምርመራ ኪት ለማግኘት COVID.gov በፖስታ ሊታዘዝ ይችላል። የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) ተማሪዎች፣ የቤተሰብ አባላት እና ሰራተኞች እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ ላይ የኮቪድ-19 ክትባቶችን ትምህርት ቤት-በሚገኙ ክሊኒኮች መውሰድ ይችላሉ፣ ይህ አገልግሎት ከበዓል እረፍት በኋላ ይቀጥላል።
ትምህርት የመማር መቆራረጥን መቀነስ
ቀጣይነት ያለው ትምህርት እና አስተማማኝ ክትትልን ለማስቀጠል ተጨማሪ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ትምህርት ቤቶችን ለመለየት MCPS የኮቪድ-19 ስርጭት ሁኔታዎችን እና የሰራተኞች እና የተማሪ መቅረት አዝማሚያዎችን ጨምሮ በርካታ እርምጃዎችን ይከታተላል። ቀደምት ጣልቃገብነቶች ለማህበረሰብ በቅድሚያ ማሳወቅ፣ የአካባቢ የኢንፌክሽን ቁጥጥር እርምጃዎችን ማስፋፋት እና ተጨማሪ የሰራተኞች ድጋፍ እና ሌሎች እርምጃዎችን ያካትታሉ። እነዚህ መስፈርቶች እና በት/ቤት ደረጃ በድንገተኛ ጊዜ ቨርቹወል ትምህርት የመስጠት እቅዶች MCPS 2022-2023 የመልሶ መክፈቻ መመሪያ ውስጥ ተገልጸዋል።
ባለፉት ሁለት የትምህርት ዓመታት አብረን የተሻገርናቸውን ታይቶ የማይታወቅ ፈተናዎችን መለስ ብለን ስንመለከት፣ 2023 ደስተኛ - የበለጠ ጤናማ - እና በልበ ሙሉነት የምንሻገርበት ዓመት እንደሚሆን እንጠባበቃለን።
ከልብ
Patricia Kapunan, M.D., M.P.H.
MCPS Medical Officer
Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org