December 22, 2022

የተከበራችሁ የ MCPS ማህበረሰብ፦

ዛሬ፣ ስለ ጤንነት/ደህንነት እና በመማር ማስተማር ላይ ባለን ቁርጠኝነት የመተንፈሻ አካላት በሽታዎች ሊያስከትሉ የሚችሉትን ተፅእኖዎች በመቀነስ ረገድ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስን (MCPS) ጥረት አጋራችኋለሁ። እነዚህ ጥረቶች የሚያተኩሩት የመተንፈሻ አካላት ላይ የሚተላለፍ ቫይረስ ስርጭትን በመቀነስ፣የኮቪድ-19 ስርጭትን በመቆጣጠር በትምህርት ቤቶች ውስጥ ስርጭትን ለመቀነስ እና የትምህርት ማቋረጥን በመቀነስ ላይ ነው። የማህበረሰባችንን የጤና አጠባበቅ አዝማሚያዎችን ለመከታተል እና ለህብረተሰባችን ግብዓቶችን እና ድጋፍ ለመስጠት ከሞንትጎመሪ ካውንቲ የጤና ጥበቃ እና ሰብአዊ አገልግሎት ዲፓርትመንት (DHHS) ጋር በቅርበት መስራታችንን እንቀጥላለን።
የአሁኑ ክረምት በህብረተሰብ ጤና ላይ አዳዲስ ፈተና ይዞ መጥቷል። ኮቪድ አሁንም ከእኛ ጋር አለ፣ በመከላከል እና በህክምና ብዙ መሻሻሎች ቢኖሩም፣ እንደ ኢንፍሉዌንዛ እና የመተንፈሻ አካል በሽታ RSV የመሣሰሉ ሌሎች ቫይረሶች በአካባቢያችን እና በክልላችን ላይ የተደራረበ የጤና ችግር እየፈጠሩ ናቸው።

በት/ቤቶች ውስጥ የመተንፈሻ አካላት በሽታ ስርጭትን መቀነስ

  • የኮቪድ-19 እና ሌሎች የመተንፈሻ አካላት ቫይረሶች ስርጭትን ለመቀነስ እንዲረዳ ጥሩ የእጅ ንፅህና፣ ሳል እና ማስነጠስ ሲኖር አፍና አፍንጫን መሸፈን እና በታመሙ ጊዜ ከሌሎች መራቅን የመሳሰሉ ጤናማ ባህሪያትን እንዲተገብሩ ማሳሰብ እና መደገፍ እንቀጥላለን።
  • ከምስጋና በዓል ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ የኮቪድ-19 በሽታ ስርጭት ሲጨምር፣በሞንትጎመሪ ካውንቲ ማህበረሰብ የበሽታው ስርጭት ስጋት ወደ መካከለኛ ደረጃ አድጓል። የጤና አገልግሎት ዲፓርትመንታችን በተጨናነቁ የቤት ውስጥ ክፍሎች ማህበራዊ ርቀቶች እንዲጠበቁ እና በደንብ የሚገጥም የአፍና የአፍንጫ የፊት መሸፈኛ ጭምብል መጠቀም እንደሚያስፈልግ በጥብቅ ይመክራል።
  • በዚህ ጊዜ በርካታ የመተንፈሻ አካላት ቫይረሶች በማህበረሰባችን ላይ የሚያሳድሩትን ተፅእኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ሰራተኞች እና ተማሪዎች ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ ጭምብል የሚያደርጉት በጥብቅ ይበረታታሉ፣በተለይ የጉንፋን ወይም ሳል ምልክቶች ካጋጠማቸው፣ከፍተኛ ተጋላጭነት ባላቸው ሁኔታዎች ውስጥ ወይም በመተንፈሻ አካላት በሽታ ለከባድ ችግሮች ተጋላጭ ከሆኑ ጭምብል ይጠቀሙ። ካለፉት የበዓላት እረፍት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ከተመለሱ በኋላ ባሉት 2 ሳምንታት ውስጥ ከፍተኛ ተላላፊ የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን የመያዝ ስጋት አይተናል።

የኮቪድ-19 ስርጭት እና ተጋላጭነትን መቆጣጠር
በትምህርት ቤቶቻችን ውስጥ የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመቀነስ ምርመራ ማድረግ ወሳኝ መንገድ ነው።

  • ሁሉም ሰራተኞች እና ተማሪዎች ለበዓል እረፍት ወደ ቤታቸው እንዲወስዱ የምርመራ እቃዎች ለትምህርት ቤቶች እና የስራ ቦታዎች ተሰራጭተዋል።
  • ሠራተኞች እና ተማሪዎች ከበዓል እረፍት በኋላ ወደ ት/ቤቶች ከመመለሳቸው በፊት ምርመራ እንዲያደርጉ በጥብቅ እናበረታታለን፣ በተለይም የበሽታው ምልክት ካላቸው እና/ወይም ኮቪድ-19 የተጋለጡ ከሆነ ምርመራ እንዲያደርጉ አጥብቀን እንመክራለን።
  • በኮቪድ-19 የተያዙ ሰራተኞች ወይም ተማሪዎች ውጤታቸውን MCPS ኮቪድ-19 ሪፖርት ማቅረቢያ ቅጽ ላይ ሪፖርት ማድረግ እና CDC ራስን የማግለል መመሪያዎችን መከተል አለባቸው። በራሳቸው ሪፖርት ስለሚደረጉ ሁኔታዎች ሪፖርት ማቅረቢያው MCPS ኮቪድ-19 ዳሽቦርድ ላይ ተገልጿል።

በትምህርት ቀን ሊሆኑ የሚችሉ የኮቪድ-19 ምልክቶችን የሚያሳዩ ተማሪዎችን ምርመራ ማድረጋችንን እንቀጥላለን፣ እና DHHS ጋር በኮቪድ-19 ምርመራ እና ወረርሽኙ እንዳይስፋፋ የመግታት አጋርነታችንን እንቀጥላለን። DHHS ነፃ የኮቪድ-19 የክትባት ክሊኒኮችን እና የሞንትጎመሪ ካውንቲ ነዋሪዎችን ይመረምራል፤ ነፃ የምርመራ ኪት ለማግኘት COVID.gov በፖስታ ሊታዘዝ ይችላል። የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) ተማሪዎች፣ የቤተሰብ አባላት እና ሰራተኞች እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ ላይ የኮቪድ-19 ክትባቶችን ትምህርት ቤት-በሚገኙ ክሊኒኮች መውሰድ ይችላሉ፣ ይህ አገልግሎት ከበዓል እረፍት በኋላ ይቀጥላል።

ትምህርት የመማር መቆራረጥን መቀነስ

ቀጣይነት ያለው ትምህርት እና አስተማማኝ ክትትልን ለማስቀጠል ተጨማሪ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ትምህርት ቤቶችን ለመለየት MCPS የኮቪድ-19 ስርጭት ሁኔታዎችን እና የሰራተኞች እና የተማሪ መቅረት አዝማሚያዎችን ጨምሮ በርካታ እርምጃዎችን ይከታተላል። ቀደምት ጣልቃገብነቶች ለማህበረሰብ በቅድሚያ ማሳወቅ፣ የአካባቢ የኢንፌክሽን ቁጥጥር እርምጃዎችን ማስፋፋት እና ተጨማሪ የሰራተኞች ድጋፍ እና ሌሎች እርምጃዎችን ያካትታሉ። እነዚህ መስፈርቶች እና በት/ቤት ደረጃ በድንገተኛ ጊዜ ቨርቹወል ትምህርት የመስጠት እቅዶች MCPS 2022-2023 የመልሶ መክፈቻ መመሪያ ውስጥ ተገልጸዋል።

ባለፉት ሁለት የትምህርት ዓመታት አብረን የተሻገርናቸውን ታይቶ የማይታወቅ ፈተናዎችን መለስ ብለን ስንመለከት፣ 2023 ደስተኛ - የበለጠ ጤናማ - እና በልበ ሙሉነት የምንሻገርበት ዓመት እንደሚሆን እንጠባበቃለን።

ከልብ

Patricia Kapunan, M.D., M.P.H.
MCPS Medical Officer



Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org

Montgomery County Public Schools