እሴቶቻችንን እና ለቤተሰቦች ያለንን ድጋፍ እንደገና ማረጋገጥ

ውድ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) ቤተሰቦች

በቅርብ ጊዜ በአካባቢውም ሆነ በመላ አገሪቱ እየተከናወኑ ያሉት የፌዴራል የኢሚግሬሽን ማስፈጸሚያ እርምጃዎች ለብዙ የማህበረሰባችን አባላት ስጋት መፍጠራቸውን እንገነዘባለን። ለአንዳንዶች፣ ዜናውን ማድመጥና መመልከት እንኳን ከባድ ሊሆን ይችላል። ይህንን የጻፍነው ባለፈው ዓመት እና በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ እንደገለጽነው፣ እሴቶቻችንን ለማጠናከር እና አንዳንድ ጠቃሚ መረጃዎችን ለእናንተ ለማጋራት ነው። በቀላል አነጋገር፣ ተማሪዎቻችንን እና ቤተሰቦችን ለመደገፍ ቁርጠኛ ነን። 

የእኛ ቁርጠኝነት

ትምህርት ቤቶቻችን ለልጆች ደህንነታቸው የተጠበቀ እና አስተማማኝ ቦታዎች መሆናቸውን ለማረጋገጥ የሞንትጎሞሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) ሰራተኞች በየቀኑ ጠንክረው ይሰራሉ። እያንዳንዳቸው ተማሪዎች፣ የኢሚግሬሽን ሁኔታቸው ​​ምንም ይሁን ምን፣ በሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ ውስጥ ተቀባይነት አላቸው፣ ዋጋ አላቸው፣ እንክብካቤ ይደረግለቸዋል፣ እና የሚወደዱ ናቸው። ይህ በሜሪላንድ እና በመላው ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥም ተግባራዊ የሆነ ሕግ ነው።

ሁሉም ልጆች ሕዝባዊ ትምህርት የማግኘት መሠረታዊ መብት አላቸው፣ እና በፌዴራል ሕግ ድንጋጌ መሠረት እያንዳንዱ ልጅ ከመዋዕለ ህጻናት እስከ 12ኛ ክፍል (K-12) ትምህርት የማግኘት መብት ያለው/ያላት መሆኑን ያረጋግጣል። የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ በምዝገባ ወቅትም ሆነ በሌላ በማንኛውም ጊዜ ስለ ኢሚግሬሽን ሁኔታ አይጠይቁም። በፌዴራል ሕግ መሠረት የተማሪዎችን ግላዊነት እንጠብቃለን እንዲሁም በቤተሰብ የትምህርት መብቶች እና የግላዊነት ሕግ (FERPA) መሠረት የተማሪዎችን የመረጃ ፋይሎች እና የግል መረጃዎችን በጥብቅ እንጠብቃለን።

የፌዴራል ሕግ አስከባሪ አካላት ወደ ትምህርት ቤት ቢመጡ ምን ይከሰታል?

ዲስትሪክቱ የኢሚግሬሽን ወይም ሌላ የፌዴራል የህግ አስከባሪ እንቅስቃሴ በትምህርት ቤት አቅራቢያ ወይም በትምህርት ቤት ውስጥ ቢከሰት ግልጽ የሆኑ ተግባራዊ ሂደቶች አሉት። እነዚህ ሂደቶች የተነደፉት እንደሚከተለው ነው፦

  • የተማሪዎችን ደህንነት እና ሠላም ቅድሚያ መስጠት፣

  • ሕግ መከበሩን ማረጋገጥ፣ እና

  • ከቤተሰቦች ጋር ግልጽ የሆነ ግንኙነት ማድረግ።

ህጋዊ የፍርድ ቤት ትዕዛዞችን ማክበር ቢኖርብንም፣ MCPS በኢሚግሬሽን ማስፈጸሚያ እርምጃዎች ውስጥ አይሳተፍም። እናም የኢሚግሬሽን አስከባሪዎችን ወደ የትኛውም ትምህርት ቤቶቻችን በፍጹም አንጋብዝም። ይልቁንም የእኛ ኃላፊነት ሁሉንም ተማሪዎች ማስተማር እና ትምህርት ቤቶቻችን ለተማሪዎችና ለሠራተኞች አስተማማኝ ምቹ ቦታዎች መሆናቸውን ማረጋገጥ ነው። 

የቤተሰቦች ድጋፍ እና ግብዓቶች

ቤተሰቦች መረጃ እና አስተማማኝ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው እንረዳለን። MCPS ለቤተሰቦች "መብትዎን ይወቁ"/“Know Your Rights” መረጃ ለመስጠት፣ የህግ አገልግሎት ግብዓቶችን እና ከማህበረሰብ የድጋፍ አገልግሎት ሰጪዎች ጋር ለማገናኘት "CASA and the Gilchrist Immigrant Resource Center" የመሳሰሉ የማህበረሰብ አጋሮች ጋር ይሰራል። አብዛኛው መረጃ በዚህ ድረ ገጽ ላይ ይገኛል። 

ስለዚህ ጉዳይ ከወጣት የቤተሰብ አባላት ጋር መነጋገር አስቸጋሪ ሊሆን ቢችልም፣ እነዚህን ውይይቶች ለማገዝ ከሚታመኑ አጋሮቻችን እና MCPS ሪሶርሶችን እንዲያገኙእናሳስባለን። 

ቤተሰቦች በቀጥታ MCPS አለም አቀፍ የተማሪዎች ምዝገባ እና መቀበያ ቢሮ ጋር በመገናኘት ከሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ እርዳታ ማግኘት ይችላሉ፣ ከዚያም ሰራተኞች መመሪያ ሊሰጡዋቸው እና ተገቢ ድጋፍ ወደሚያገኙበት ሊያገናኙዋቸው ይችላሉ። ይህንን ቢሮ የስልክ ቁጥር 240-740-4500 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፣ ወይም በዚህ አድራሻ ወደቢሮ በመሄድ ሊያገኟቸው ይችላሉ፦ Rocking Horse Road Center (RHRC), 4910 Macon Road - Suite 147, Rockville, MD 20852

የቪዲዮ መልዕክቱን ይመልከቱ

ስለ ቁርጠኝነቶቻችን፣ ፕሮቶኮሎቻችን፣ እና ሪሶርሶቻችን ተጨማሪ መረጃ እና ማረጋገጫ ለማግኘት የቪዲዮ መልዕክቱን እንዲመለከቱ እናበረታታዎታለን።


ቪዲዮ ይመልከቱ

ከሠላምታ ጋር

Grace Rivera-Oven
የትምህርት ቦርድ ፕሬዚደንት

Thomas W. Taylor, EdD MBA
Superintendent of Schools

ሪሶርሶች



በዚህ አድራሻ ኢሜል ይላኩልን፦ ASKMCPS@mcpsmd.org